አምራች ኢንዲስትሪያሊስቶች በሁለንተናዊ ዘርፉ የሚያጋጥማቸውን ተግዳሮቾች በመፍታት የሃገር ኢኮኖሚን ከመደገፍ ባለፈ ሃገራችንን የአፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ለማድረግ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት የሚጠበቅባቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ።
ኢትዮጵያ ከልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ለውጪ ሀገር ገበያ ከሚቀርብ የኢንዱስትሪ ምርት አንድ ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሰሀ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ።
በኢትዮጵያ የሚገኙ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለሀገር ልማት ያበረከቱትን አስተዋጽኦ እና ሊያጋጠሙ በሚችሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ የምርምር ወርክሾፕ ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ዘላቂ መሰረት እንዲኖረውና ለሃገር የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ለማሳደግ አነስተኛና መካከለኛ አምራቾችን በልዩ ሁኔታ መደገፍ እንደሚገባ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽን እና ፓርክ አስተዳደር ዘርፍ ስራ አስፈጻሚ ፍጹም ከተማ ገለጹ፡፡